Wednesday 31 October 2012

ብርሃንና ሰላም = ጽልመትና ሽብር

ከሰሎሞን ተሰማ ጂ.
(semnaworeq.blogspot.com)
“ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት፣ ሳምንታዊውን የፍትሕ ጋዜጣ እንዳይሰራጭ አገደ፤” (www.fetehe.com እና በአዲስጉዳይ መጽሔት፣ ሐምሌ 2004 ዓ.ም)
“ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት፣ ሳምንታዊው የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ እንዳይታተም ከለከለ፡፡” (www.fnotenetsanet.com እና amharic.voanews.com October 02, 2012/ መስከረም 22 ቀን 2005 ዓ.ም)
“ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት፣ የሪፖርተር ጋዜጣን ገጽ ቁጥር ገደበ፡፡” (ሪፖርተር ጋዜጣ፣ ጥቅምት 4 ቀን 2005 ዓ.ም)

ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት በሁሉም ዜናዎች በበጎ ጎኑ አልተነሳም፡፡ “እንዳይሰራጭ አገደ!”እንዳይታተም ከለከለ!” እና “ቁጥር ገደበ!” የሚሉት ሃረጎች የማተሚያ ቤቱን ስምና ክብር የሚያጎድፉ ናቸው፡፡ ይህ ማተሚያ ተቋም፣ የዛሬዎቹ ሹመኞችና ባለሥላጣናቱ አወቁትም – አላወቁትም ትልቅ ራዕይና አላማዎችን አንግቦ የተነሳ ነበር፡፡ እነዚህን ተልዕኮዎቹን ለርካሽ የፖለቲካ ትርፍ ሲባል መስዋዕት ማድረግ ግን ከተጠያቂነትና ከታሪክ-ሕሊና ተወቃሽነት አያድንም፡፡
“ብርሃንና ሰላም የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ማተሚያ ቤት” በመስከረም 3 ቀን 1914 ዓ.ም በአልጋ ወራሽ ተፈሪ መኮንን ተቋቋመ፡፡ ይህ ማተሚያ ቤት በጥቃቅን ፔዳሎች ማለትም በእግር በመርገጥ በሚንቀሳቀሱ የማተሚያ መኪናዎች ሥራውን የጀመረው ስድስት ኪሎ በሚገኘው የዛሬው የቋንቋዎች አካዳሚ ሕንፃ ውስጥ ነበር፡፡ 

ዛሬነገ ሳንል መነሳት የዜግነትግዴታችን ነው!

  ለቀድሞው  የወያኔ  ጠቅላይ ሚኒስትር  ለጊዜው  ኳሷ  በእሳቸው ቁጥጥር ስር እንደሆነች እና የኢትዮጵያ ህዝብን ፍላጎት ማክበር አለበለዚያም የኢትዮጵያ ህዝብ እና ታሪክ ጠላት
አብዶ ኑር ዮሱፍ (ኖርዌ)
  ሆነው  የመቀጠል ሁለት ምርጫ እንዳላቸው  በኢትዮጵያ ምሁራን  በየአቅጣጫው  ቢነገራቸውም ፤  በማን አለብኝነት ኳሷን  ባለማከፋፈል ችግር  ፣  እኔ ብቻ  በኳሷ  እንደፈለኩ  ከምፈልገው  ወገን ጋር  ልጫወትባት ፣ ስለ ኳሷ አትጠይቁኝ ፣ ወደ ኳሷም አትጠጉ በማለት ቀይ መስመር በማስመር እና እኔ ብቻ አውቃለሁ በማለት  በ 80 ሚሊዮን ህዝብ  ራእይ እና  ተስፋ  ላይ  እንደቀለዱ  እንዲሁም  ስልጣን  ላይ  ሙጭጭ እንዳሉ  እና  ኳሷን ያለአግባብ  በቁጥጥራቸው  ስር  በማዋል  ብሎም የኢትዮጵያ ህዝብ  መተንፈስ እንኳን እንዳይችል  አድርገው  በፍርሃት አስረው  በማስቀመጥ  በማን አለብኝነት ጢባ ጢቦ  እየተጫዎቱ  ባሉበት ወቅት  ባልትጠበቀ ሁኔታ  ጊዜው ደርሶ  ወደ ማይመለሱበት  አለም አምልጠዋል  ፡፡ በስሩት ወንጀል  በአለም አቀፍ  ፍርድ ቤት  ሳይጠየቁ  ማምለጣቸው ቢያስቆጭም፡፡
 

Tuesday 30 October 2012

የኦሮሞ ፖለቲካ ጉዳይ (ከትናንት እስከ ዛሬ)


 የኦሮሞ ፖለቲካ ጉዳይ (ከትናንት እስከ ዛሬ)
አቶ  ቡልቻ ደመቅሣ

የኦሮሞ የፖለቲካ ጉዳይ በየዘመኑ አንድ እርምጃ ወደፊት ሁለት እርምጃ ወደኋላ ሲመሏ ለዘመናት ቆይቷል፡፡ ይህ የሆነው ከአፄ ሚኒሊክ ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡ ከዚያ በፊት፣ የኢትዮጵያ ነገስታት ኦሮሞን ለማሸነፍ ስላልቻሉ በየጊዜው እየተጋጩ እንደምንም አብረው ይኖሩ ነበር፡፡ ፋዘር አልሜዳ የሚባለው የፖርቱጋል ቄስ በዚህ ጉዳይ በሰፊው ጽፏል፡፡ ነገር ግን አብሮነታቸው እንደ ገዥና ተገዥ አልነበረም፡፡ ከአጼ ልብነድንግል ጀምረው እስከ ንጉስ ሳህለ ስላሤ የነበሩት አፄዎች ሁሉ ኦሮሞን ለማሸነፍ እና ለመግዛት ያላደሩጉት ጥረት አልነበረም፡፡

የኢትዮጵያዋ፡ ርእዮት ‹‹የጥንካሬዬ ዋጋ››

ከፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም
 ትርጉም ከነጻነት ለሃገሬ


 ስለስልጣን ብልግና አለያም ስለ ስልጣንን በማንአለብኘነት አለ አግባብ ስለ ከመጠቀም ከመናገር ይበልጥ አስቸጋሪ የሆኑ ብዙ ነገሮች የሉም፡፡ ለ31 ዓመቷ ወጣት ኢትዮጵያዊትReeyot Alemu, the 31 year-2012 Courage in Journalism Award winner. አይበገሬ ርዕዮት ዓለሙ ግን፤ የመጻፍ ነጻነት፤ የመናገር ነጻነት፤ ሃሳብን በነጻ የማንሸራሸር ነጻነትን ድምጻቸው በመሳርያና በስለላ መዋቅር ለታፈነባቸው ድምጽ ከመሆን ምንም አይነት ጋሬጣ ቢደረደር ሊያደናቅፋት ጨርሶ አይችልም፡፡

 አሁንም ቢሆን ባለችበት ክፉ ሁኔታም ሆና ስለግፍ ስልጣን ቁልጭ ያለ ሃቅን ትናገራለች፤ ‹‹ለጥንካሬዬ ዋጋ እንደምከፍል ብገነዘብም የሚቃጣብኝን ለመቋቋም ዝግጁ ነኝ››፡በማለት ካለችበት ገሃነማዊ የቃሊቲ ጉረኖ ባመለጠው የእጅ ጽሁፏ መልእክቷን ለአለም አስተላልፋለች፡፡ “ጥንካሬ ለሁሉም ድርጊት ታላቅ ዋጋ አለው፡፡ 
ጥንካሬ ከሌለ ማንኛውንም አይነት ዋጋ ያለው ተግባር ማከናወንም ሆነ ማቀድ አይቻልም” ያለችው ታላቋ የአሜሪካ የሰብአዊ መብት ተሟጋችና ጸሃፊ ማያ አንጀሉ ናት፡፡ ባለፈው ሳምንት የዓለም አቀፉ ሜዲያ ፋውንዴሽን (IWMF) የ2012ን ታላቁን “የጋዜጠኝነት ጀግንነት” ሽልማቱን ለአይበገሬዋ ርዕዮት ዓለሙ ሸልሟል፡፡ ባለፈው ሜይ ርዕዮትን ወደ ወህኒ ለመወርወርና ዝም ለማሰኘት ስለተከናወነው ሂደት ጽፌ ነበር፡፡ ለዚያ ማፈርያ ፍርድ ቤት ማስረጃ ተብሎም በርዕዮት ላይ የቀረበው ሰነድ፤ከሌሎች የሙያ ባልደረቦች ጋር በህገወጥነት የተሰበሰበ የኢሜይል ልውውጥ፤በስለላ መዋቅሩ የተጠለፈ የቴሌፎን ንግግር፤ሲሆን ከሁሉም ጋር ያደረገችው ልውውጥ ግን ሰላማዊ ትግልና ለማጠናከር ሊደረግ የሚገባውን የሚያመላክት ብቻ ነበር፡፡