Wednesday 30 October 2013

የአቶ መለስ ዜናዊ “ያልተገለጡ ገፆች”

October 29, 2013

ከበትረ ያዕቆብ
ዉድ የሀገሬ ልጆች ከሁሉም በማስቀደም እንደምን ናችሁ ? ደህና ናችሁ ? 2006 እንዴት ይዟችኋል ? ስል የጠበቀ የወዳጅነት ሰላምታየን ማቅረብ እወዳለሁ፡፡ እዚህ ላይ ይህ ሰዉ ምን ነካዉ!? ባልተለመደ መክኩ ሰላምታ አበዛሳ !? ልትሉ ትችላላችሁ፡፡ ሆኖም አትፍረዱብኝ፡፡ “አሸባሪ ፣ አክራሪ ፣ ጅሀዳዊ ፣ ተለጣፊ ፣ ነጭ ለባሽ”… ወዘተ የሚል ቅፅል ስም ለሀገር ወዳድና ለመብታቸዉ መከበር ድምፃቸዉን ለሚያሰሙ ሁሉ በጅምላ እየተሰጠ ዜጎች በሀሰት በሚወነጀሉበት ሀገር ፤ በእያንዳንዷ ቀን እንደ መልካም ተግባር መሰል ዜጎችን ጠልፎ ለመጣል የተንኮል ወጥመድ ሲጠመድ በሚዋልበት ጊዜ ፣ ንፁህ ዜጎች በግዳጅ ያልፈፀሙትን ኃጢያት እንዲናዘዙ በሚገደዱበት ዘመን ፤ በልቶ ማደር ፍፁም በከበደበት በዚህ የጭንቅ ወቅት አጥብቆ ደህንነትን መጠየቁ ተገቢ ሆኖ ስለታየኝ ነዉ፡፡ እንደዉም ከዚያም በላይ ብዙ ብል እንኳ የሚበዛ አይመስለኝም፡፡ የሆነ ሆኖ ለሰላምታ ያህል ይህን ካልኩ ወደ ዋናዉ ርዕሰ ጉዳየ በቀጥታ ልለፍ፡፡

ኢትዮጵያ- የፖሊስ መንግስት ያንሰራፋባት ሀገር (ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረ ማርያም)

October 30, 2013

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረ ማርያም
ትርጉም ከነጻነት ለሀገሬ
horrors that take place in the little shop of horrors of the ruling regime in Ethiopiaየኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ህገመንግስት በህግ ከለላ ጥላ በቁጥጥር ስር የሚውሉ ዜጎችን አስመልክቶ የሚከተሉትን መብቶች ያጎናጽፋል፡፡“በህግ ከለላ ጥላ በቁጥጥር ስር የዋለ ማንኛውም ሰው በህግ አግባብ መብቱ ተጠብቆ ይያዛል፡፡ ማንኛውም ሰው በሀሰት ለመረጃ ጠቀሜታ ተብሎ በማስገደድ እንዲያምን  ወይም የተባለውን እንዲቀበል አይገደድም፡፡ ማንኛውም በማስገደድ የተገኘ መረጃ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡“ ይላል አንቀጽ 19(2)(5)፡፡ እውነታው ሲታይ ግን ይህ የይስሙላ ሙበት የተጻፈበትን ወረቀት ዋጋ ያህል የለዉም፡፡

ባለፈው ሳምንት ሂዩማን ራይትስ ዎች “HRW“ የተባለው ዓለም ዓቀፋዊ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት በኢትዮጵያ መንግስት “የፌዴራል ፖሊስ ማዕከላዊ ምርመራ” እየተባለ በሚጠራው የፖሊስ ጣቢያ የሚፈጸሙትን አስደንጋጭና አስከፊ የሰብአዊ መብት ረገጣዎች ዘገባ ሪፖርት አቅርቧል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘው ይህ የፖሊስ ምርመራ ማዕከል በጥርጣሬ የተያዙ ዜጎችን በማሰቃየት ይታወቃል፡፡

Monday 21 October 2013

ኦብነግ በመንግስት ባለስልጣናት ላይ ጥቃት መፈጸሙን አስታወቀ

ኢሳት ዜና :-የኦጋዴን ነጻ አውጭ ድርጅት በም/ጠ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በሚመራው የልኡካን ቡድን ላይ ጥቃት ፈጽሞ በርካታ ወታደሮችን መግደሉን የግንባሩ ቃል አቀባይ ለኢሳት ገለጹ።
አቶ ሀሰን አብዱላሂ እንደገለጹት ጥቃቱ የተፈጸመው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የ9 የክልል መሪዎችንና ባለሀብቶችን አስከትለው በአካባቢው ጉብኝት ለማድረግ ቀብሪደሀር አየር ማረፊያ ባረፉበት ወቅት ነው።

Candle lighting for the victims of refugees in Lampedusa in italia

Sunday 20 October 2013

ህውሃት ኢሃደግ መንግስት በልጆቼ ለምን ዘመተ? (ከኣስገደ ገ/ስላሴ ወ/ሚካኤል)

  1. Photo: አስገደ ገብረስላሴና በእስር እየተሰቃዩ ያሉ ልጆቹ።
ሁለተኛ ልጄ ክብሮም እንደ ወንድሞቹ የእስር ሰለባ ሆነ፡፡እኔ ለኢትዮፕያ ህዝብ ጠላት ሳልሆን ፍፁም ወዳጁ ነኝ መጀመርያ ደርግን 17 ኣመት በመታገል ፋሽሽታዊ ደርግ በማስውግድ ኣስተዋፅኦ ነበረኝ፡፡ ህውሃት ኢህኣደግ ስልጣን ከያዘ በሃላም ለንሮየ ለደሞወዝ ሳላስብ 17 ኣመት ሙሉ የታገልኩበት ኣላማ ስለተቀለበሰ በተጨማሪ የህውሓት መሪዎች ለኢቲዮፕያ ሉኣላዊነትና ኣንድነት ታማኝነት ስላጎደሉ የኢትዮፕያ ሕገመንግስት በሚፈቅደው መሰረት በግልም በፓርቲ ተደራጅቼ እየታገልኩ ቆይቼ ኣሁንም እታገላለው ታድያ እኔ በሃገራችን ሕ/መንግስት በሚፈቅድልኝ መሰረት መታገሌ እንደ ሃጠያት ተቆጥሮ የቂም በቀል ፖለቲካ ወደ ልጆቼ ምን ኣመጣው ይህ ለማለት የፈለጉኩት፡፡

Wednesday 16 October 2013

The Fading Political Cult (Sadik Ahmed)

September 28, 2013

by Sadik Ahmed
Meles was an administrative felon who turned his elegance to one giant political orphanage. As Meles departed unexpectedly, the scream from his political orphanage is wandering throughout the world wherever his cult followers are. Unlike other well-known leaders, Meles has not attached himself to a smart life partner; he picked out not book-smart but street–smart, and uncivilized ghetto style spouse, who can fit the scam but not the dictatorial dwelling as a first lady.

Breaking News Oct 16, 2013

ለአፍሪካ ፈላጭ ቆራጭ ገዢዎች ፍትሕ አይቀሬ ናት


international criminal court
October 16, 2013
ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም ከነጻነት ለሃገሬ
ማስታወሻ ለአንባቢው፡፡ ባለፈው ሳምንት ሐተታዬ ‹‹የዘር አደን›› በሚል አሉባልታዊ ክስ  የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት በተሰነዘረበት ክስ ደግፌው ተሟግቼለታለሁ፡፡ በዚህም ሳምንት ድጋፌን በመቀጠል እነዚህ ፈላጭ ቆራጭ ገዢዎች የፈጠሙትን ግፍና በደል ጭቆና በመዘርዘር ራሳቸውን ነጻ በማድረግ የአይ ሲ ሲን (የኣለም ወንጀለኛ ፍርድ ቤት) ስም በማብጠልጠልና የቆመለትን ዓላማ የሳተ በማስመሰል ገዢዎችና አስፈጻሚዎ ቡችሎቻቸው ያነሱዋቸውን ማስረጃ ቢስ ውንጀላዎች በተጨባጭ ማስረጃ ድርጊቶታቸውንና ሸፍጣቸውን ይፋ ለማድረግ ወስኛለሁ፡፡ የኦክቶበር 11-12, 2013 የአፍሪካ አንድነት ‹‹መሪዎች›› የጨረባ ስብሰባ የተጠራውም ቴአትራዊ የልብ ወለድ ሴራ ለማካሄድና ነጻ ለመምሰል የሚያስችላቸውን ቅጥፈት ለማናፈስ ነው፡፡

Monday 14 October 2013

Bomb blast in Ethiopian capital kills two: state radio

By Aaron Maasho

ADDIS ABABA |
(Reuters) - A bomb blast in the Ethiopian capital Addis Ababa killed two people on Sunday, state radio said.
There was no immediate claim of responsibility for the bombing, but Ethiopia says it has thwarted plots of attacks in the past two years and blames rebel groups based in the south and southeast, as well as Somalia's al Shabaab insurgents.

Sunday 13 October 2013

ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ሲኤንኤን በየአመቱ የሚያዘጋጀው የአፍሪካ ጋዜጠኞች ሽልማት ተበረከተለት፡፡


wtt</a
ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ አሸናፊ የሆነበትና ሲኤንኤን በየአመቱ በሚያዘጋጀው መልቲቾይስ የአፍሪካ ጋዜጠኞች ሽልማት ስነስርዓት እየተካሄደ ነው፡፡
ባለቤቱ መምህርት ብርሀን ተስፋዬ እና ልጁ ፍትህ ውብሸት በደቡብ አፍሪካ ኬፕ ታውን ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር ተገኝተው ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ሽልማቱን ተቀብለዋል፡፡ የሽልማት ስነስርዓቱ በ45 የአፍሪካ ሀገራት በቀጥታ እየተላለፈ ይገኛል፡፡

Zehabesha Breaking News: Sebhat Nega and his bodyguards attacking peacef...

ይድረስ ለፕሬዚደንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ

October 10, 2013

 President Girma Wolde-Giorgis
ይሄይስ አእምሮ
ክቡር ፕሬዚደንት ግርማ ሆይ፣
ኢትዮጵያንና “ሕዝቦቿ”ን የሚወዱ ከሆነ ቀጥዬ የምነግርዎትን ከልብ እንዲሰሙኝ በሚያምኑት እለምነዎታለሁ፡፡
ሰሞኑን በጡረታ ሊሰናበቱ እንደሆነ ከተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ዜና ዘገባ ሰማሁ፡፡ በመጀመሪያ ሥራዎን ጨርሰው ለዚህ በመብቃትዎ እንኳን ደስ ያለዎ፡፡ ቀጥዬም በሥራ ዘመንዎ ምን እንደሠሩና እኛ በምናውቅልዎም ሆነ እርስዎ በሚያውቋቸው ምክንያቶች የተነሣ ምን ምን መሥራት ፈልገው ሊሠሩ እንዳልቻሉ “ፕሬዚደንታዊ የሥልጣን ዘመን”ዎን የኋሊዮሽ በማሰብ  ከራስዎ ጋር በምልሰት ለመነጋገር የሚያስችል የማሰላሰያ ጊዜ በማግኘትዎ አሁንም በድጋሚ እንኳን ደስ ያለዎ – መልካም ዕረፍት፡፡ 

ስብሃት ነጋ ወንጀል ፈፀሙ፤ በአሁን ሰአት በፖሊስ እየታደኑ ነው

sebehat nega one of the founders of TPLF

October 13, 2013

ከኢየሩሳሌም አርአያ
በአሌክሳንደሪያ ቨርጂኒያ ከአንድ ሰአት በፊት ስብሃት ነጋና አብሯቸው የነበረ ግለሰብ በአንድ ኢትዮጲያዊ ላይ ከፍተኛ ድብደባ ፈፅመው ማምለጣቸውን ማረጋገጥ ተችሏል። 

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ወደ ፖሊስ ጣብያ ተወሰዱ

October 11, 2013

በአሁኑ ወቅት በመነን አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ በቁጥጥር ስር የነበሩት የፓርቲ አመራሮች ወደ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ መወሰዳቸዉን አሁን የደረሰን መረጃ ይገልፃል፡፡
***
ጉዳዩ እንደዚህ ነው መንግስት ነኝ ባዩ በስራው ግን ከማፍያ ቡድን እምብዛም የማይለየው ህወሀት/ኢህአዴግ በተለየም የሰማያዊ ፓርቲ እና የአንድነት ፓርቲ አጠናክረው የቀጠሉት የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ ስጋት ውስጥ ጥሎታል።
“ሳይቃጠል በቅጠል” እንዲሉ ይህን ህዝብ ውስጥ በፍጥነት እየሰረጸ የመጣውን እንቅስቃሴ ድምጽ በሌለው መሳሪያ ለማዳከምና ብሎም ለማምከን ህወሀት/ኢህአዴግ እየተከተለ ያለው ስልት ቡድኑ ምን ያህል “የሞራል የበታችነት” እንደተላበሰ የሚያሳይ ነው።

Monday 7 October 2013

ኤርትራ በኢትዮጲያ መከላከያና ደህንነት ውስጥ ሰላዮችን ማሰማራቷን ኢትዮጲያ አመነች፥ ኢሳት ዜና

October 4, 2013

The charges under the files Fikru Abebe Haile, Tesfu Abate Abyneh, Mohmamed Umer Mohammed, Tamene  Tememte Zewde and Zerfu Melka, members of the Ethiopian Defense Forces, and accused of spying for Eritrea, reads that the Ethiopian government has admitted that it has been infiltrated by the Eritrean Intel Network built between Addis Abeba, Borena and Nairobi, Kenya, ESAT has reported tonight.

ታማኝ እና ቴዲ ትላንት ምሽት በስልክ አወሩ ምንጭ (ክንፉ አሰፋ)

ትላንት ምሽት። እለተ እሁድ፤ ኦክቶበር 6፣ 2013። ታማኝ በየነ እና ቴዲ አፍሮ በስልክ አወሩ። ንግግራቸው ከወትሮው የተለየ አልነበረም። እንደቀድሞው እየተቀላለዱ ይሳሳቃሉ። ታማኝ ከዴንቨር-ኮሎራዶ፣ ቴዲ ደግሞ ከሲድኒ-አውስትራሊያ በስራ ላይ ነበሩ። በዚህ የሶስትዮሽ የስልክ ጨዋታ ላይ እኔና ጴጥሮስ አሸናፊም ገብተናል።

Sunday 6 October 2013

አዲሱ የኢህአዴግ አሰላለፍ (ከጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ)

ኢህአዴግ ከቀድሞ ሊቀ-መንበሩ አቶ መለስ ዜናዊ ህልፈት በኋላ በተከሰተበት ውስጣዊ ልዩነት በተለዋዋጭ የኃይል ሚዛን ሥር ለማደር በመገደዱ የስልጣኑን መዘውር የሚያሽከረክረውን አካል ለመለየት አዳጋች ነበር፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ይህ ሽኩቻ መፍትሄ ማግኘቱን የሚያመላክቱ ሁናቴዎች መፈጠራቸውን የውስጥ አወቅ መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡

Journalist Temasegan Dasaleg
እንደ መግቢያ
ድንገቴው የመለስ ህልፈት ህወሓትን ቢከፍለውም፣ ብአዴን ራሱን እንዲያጠናክር መደላድል ፈጥሮለታል፡፡ ይህ የሆነበት ምክንያት መለስ ዘመኑን ሙሉ በብአዴን ታማኝነት ላይ ጥርጣሬ ስላልነበረው ቀድሞውንም እንዲዳከም ባለማድረጉ ይመስለኛል፡፡ እርሱ በአይነ ቁራኛ ይጠብቀው የነበረው ህወሓትን ነበር፤ በተለይም በሠራዊቱ እና በደህንነቱ ውስጥ ‹‹ተፅእኖ መፍጠር ይችላሉ›› የሚባሉት አቦይ ስብሃት ነጋ እና የትግራይን መዋቅር በእጁ ያደረገው የቀድሞ የክልሉ አስተዳዳሪ ፀጋዬ በርሄ በጥርጣሬ ዓይን የሚታዩ ሆነው ቆይተዋል፡፡ በምርጫ 2002ቱ ማግስትም ድርጅቱ አቦይን ‹‹በክብር›› እንዲሸኝ ሲደረግ፣ ፀጋዬ በርሄን ደግሞ ‹‹አማካሪ›› በሚል ሽፋን ከመቀሌ ወደ ቤተ-መንግስት (ጠቅላይ ሚንስትሩ ቢሮ) አዛውሮ በቅርብ እይታ ስር በማዋሉ ሁለቱንም ከጨዋታ ውጪ አድርጓቸዋል፡፡

የተቃዋሚዎች የሰላማዊ ሠልፍ ጥያቄ ከቀጠለ እንደሚቆም ገለጹ! የወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ


‹‹በኢሕአዴግ ውስጥ መከፋፈል አለ የተባለው ምኞት ነው››  ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ
የሃይማኖት አክራሪነት ትግል ፖለቲካዊ ነው አሉ
-የተቃዋሚዎች የሰላማዊ ሠልፍ ጥያቄ ከቀጠለ እንደሚቆም ገለጹ
-በኬንያ የደረሰው ጥቃት በኢትዮጵያ ላይ እንደደረሰ ይሰማናል ብለዋል
የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ሕልፈት ተከትሎ በ2005 ዓ.ም. መስከረም ወር ላይ በይፋ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጠቅላይ ሚኒስትርነት የተሾሙት አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የሥልጣን ቆይታ አንድ ዓመት አስቆጥሯል፡፡ የአንድ ዓመት የሥልጣን ቆይታቸው ከተቆጠረ ሁለት ሳምንታት በኋላ ባለፈው ዓርብ ለአገር ውስጥና ለውጭ የመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

ሙስና ያጋለጠ የህወሓት አባል ተባረረ


በትግራይ እንደርታ ወረዳ ነው። የህወሓት አባላት የሆኑ የወረዳው አስተዳዳሪዎች (የዞኑ ሓላፊ ባለበት) እርስበርሳቸው እየተገማገሙ ሳለ አንድ አባል የወረዳው አስተዳዳሪ የ10 ሺ ብር ሙስና ከህዝብ መቀበሉ ያጋልጣል። 
የህወሓት ባለስልጣናትም እርስበርስ ተነጋግረውና ተባብረው የ10 ሺ ብር ሙስና ያጋለጠ አባል እንዲባረር ወሰኑ። ተባረረ። አዎ! አብዛኛው አባል በሙስና ከተጨማለቀ የቅጣት ሰለባ የሚሆን ሙስና ያልሰራ ሰው ነው። 

ወያኔ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ በማጓጓዝ ስራ መጠመዱ ተሰማ


ከአዲስ አበባ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ የሚወስዱ አዉራ መንገዶች ታንኮችን፤ መድፎችንና ሌሎችም ከባድ የጦር መሳሪያዎችን በተሸከሙ ከባድ ወታደራዊ የጭነት ማመላለሻ ከሚዮኖች እየተጨናነቁ መሆኑን ኢሳት ቴሌቪዥንና ሬድዮ የአይን እማኞችን ጠቅሶ ዘገበ። 

Tuesday 1 October 2013

The Fading Political Cult (Sadik Ahmed)

by Sadik Ahmed

Meles was an administrative felon who turned his elegance to one giant political orphanage. As Meles departed unexpectedly, the scream from his political orphanage is wandering throughout the world wherever his cult followers are. Unlike other well-known leaders, Meles has not attached himself to a smart life partner; he picked out not book-smart but street–smart, and uncivilized ghetto style spouse, who can fit the scam but not the dictatorial dwelling as a first lady.

Ethnic cleansing in Ethiopia

Amharic speaking people seem no longer allowed to live in all parts of Ethiopia. The ruling elite are intent on cleansing them ethnically! It’s is a disgrace such a tragedy is perpetrated in this day and age and of all places in Ethiopia, a historical melting pot of all creeds and religions!