Monday, 4 February 2013
ታማኝነት ለህዝባዊ ፍቅር ሲሰግድ። ታማኝ ትናንትም ዛሬም!
02.02.2013
ታማኝ አወቀበት ….
ተፈጥሮበት
የተነሳለት ዓለማ – አስከበሮ አፈራለት
ትናት ዘርቶ – ዛሬን አፋፍቶ – አጎምርቶ – አሳመረበት፤
ነገን ለማብራት – በተግባር ቀለም ድሮ – ጽናትን ኮለበት።
ፍቅር ሰጥቶ ፍቅር – ለታሪክ ተቀበለበት
በቀለበት ተቋም፤ - አደራን ውል አዋዋለበት።
ታማኝ አወቀበት ….
ትውፊት አጽድቆ – ለዘመን ደረበለት
መሆን መቻልን – ለመቀነት ደረሰለት።
በፍቅር ስንቅ – ተስፋን አክበሮ ለራዕይ – ዳረለት
እንደ ትናንቱ ዛሬም ታማኝ … ታመነበት ….
በማስተዋል ድርሻን – በድርጊት አበቀለበት።
Sunday, 3 February 2013
ተመስገን ስለ አዲስ ታይምስ እንዲህ አለ፤ “የመለስ ራዕይ በ‹‹አዲስ ታይምስ›› መፅሄት ተተገበረ!!!” አቤ ቶክቻው
የሁላችንም መተንፈሻ የነበረችው አዲስ ታይምስ የመንግስት ውቃቢ አልወደዳትም እናም ህትመቷ ተቋርጧል። ይህንን አስመልክቶ ተመስገን ደሳለኝ ይህንን ነግሮናል። መርዷችንን እናንብበውማ፤ ቀጥል ተሜ…
ምንም ጥርጥር የለውም መለስ ዜናዊ ፍፁም አምባገነን ነበር፡፡ ምንም ጥርጥር የለውም ከአንድ ክፍለ ጦር
በላይ የተለየ ሀሳብን እና ነፃ ሚዲያን ይፈራል፡፡ ምንም ጥርጥር የለውም ወራሾቹም ሀሳቡን በነፃነት የሚገልፅን
ከመለስ በባሰ መልኩ ይፈራሉ፡፡ ይህ ፍራቻቸው ወደ ጭፍን አምባገነንነት ስለቀየራቸው መላ ሀገሪቷን ወደ ድቅድቅ
ጨለማ እየገፏት ነው፡፡
Ethiopian journalist arrested for covering Muslim protests
Authorities have cracked down on reporters and news outlets that covered
last year’s demonstrations by Muslims, seen here. (AFP/Jenny Vaughan)
(CPJ)–Ethiopian
security forces have detained for two weeks without charge the editor
of a newsmagazine and accused him of incitement to terrorism, according
to local journalists. The Committee to Protect Journalists calls on
authorities to release Solomon Kebede immediately and halt their
harassment of journalists affiliated with the weekly Ye Muslimoch Guday.
Saturday, 2 February 2013
ኢትዮጵያዊያን ሰደተኞች በአረብ ሀገር…
በየመን ስደተኛው ላይ ግፉ ቀጥሏል፡፡ ብልቱን የተቆረጠ፣ አይኑ የጠፋ፣ጆሮው የተቆረጠ፣ እግር እጃቸው የተሰበረ ልጆች ሀረጥ IOM ካምፕ ውስጥ ያለ ህክምና ይሰቃያሉ
(በግሩም ተ/ሀይማኖት)
ዕለት ከዕለት በየመን ኢትዮጵያዊያን ስደተኛ ላይ የሚሰራው ኢ-ሰብዓዊ ድርጊትና ግፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
የሳዑዲ አረቢያ መንግስት ኢትዮጵያዊያኑ ስደተኞች ወደ ሀገሬ የገቡት በየመን በኩል ነው እና ወደ ሀገራቸው ሳይሆን
ወደ የመን ነው የምመልሰው ብሏል፡፡ ማለት ብቻም አይደለ አፍሶ እያመጣ የመን መሬት ቀይ ባህር ዳርቻ እየጣላቸው
ነው፡፡ ከሳዑዲ ተመላሾቹን ገንዘብ ይዘዋል፡፡
Subscribe to:
Posts (Atom)