Saturday 20 April 2013

ሰበር ዜና፣ በአባይ ስም ዶላር ለመሰብሰብ በሲውዲን የወያኔ አምባሳደር ወደ ኖርዌይ ተጉዛ ውርደት ተከናንባ ተመልሳለች

አምባሳደሯ በሁለት ወያኔዎች ታጅባ ስለ ፓስፖርትና፣ ስለ አባይ ግድብ ቦንድ መናገር ከመጀመሯ የኖርዌይ ኢትዮጵያውያን “የለም የለም ኢትዮጵያ ውስጥ በግፍ ስለታሰሩ፣ በዘራቸው ምክንያት በሀገራቸው እየተፈናቀሉ ስላሉት ወገኖቻችን በቅድሚያ ጥያቄ አለን” በማለት አምባሳደሯን ሰንገው ይይዟታል።
ስብሰባው የወያኔዋ ተወካይ ባሰበችው መንገድ መሄድ አልቻለም። ተረበሸ።
ግርግሩ በርትቶ በመጨረሻም አምባሳደሯ እና አጃቢዎቿ በፖሊሶች ታጅበው በመጡበት እግራቸው ተመልሰዋል።
ተጨማሪ ዘገባ ይኖረናል…

No comments:

Post a Comment