Wednesday 10 July 2013

መንግስት ጉርምስናው ብሶበታል፡፡ (አሉ) አቤ ቶክቻው!!

994766_669621469720984_194746518_n
አንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፈትህ ፓርቲ  አንድነት የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት በሚል ሃይለቃል አሸባሪው “የጸረ ሽብር አዋጅ” እንዲሰረዝ እንቅስቃሴ እያደረገ ነው፡፡ የአንድነቱ ጋዜጠኛ ወዳጃችን ነቢዩ በፌስ ቡክ ግድግዳው ላይ ሰበር ዜና ብሎ እንዲህ ነግሮናል… ነብዩ በመንግስታችን ብስጭት ማለቱ ያስታውቅበታል፤ እስቲ ቀጥል ነቤ፤
ሰበር ዜና
—————
መንግስታዊ ሽፍታነት በኢትዮጵያ
—————–

ኢህአዴግ መንግስታዊ ሽፍታነቱን ገፍቶበታል፡፡ ዛሬ ጠዋት በደሴ ከተማ የቅስቀሳ ተልዕኳቸውን በመወጣት ላይ ከአዲስ አበባ የተጓዙትን የአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ዘካርያስ የማነብርሃንና የፍኖተ ነፃነት ጋዜጠኛ የሆነውን አቶ ወንደሰን ክንፈን በማገት “እንደራረር” በማለት ላይ ይገኛል፡፡
አግተው እንደራደር የሚሉት ሽፍቶች ናቸው፤ መንግስት አግቶ እንደራደር ሲል ሽፍታነቱን በአደባባይ መረጋገጡ ነው፡፡


አንድነት የፓርቲው ጽ/ቤት እስኪዘጋና አባላቱ እስርቤቶችን እስኪሞሉ ህዝባዊ ንቅናቀው ይቀጥላል፡፡ ፓርቲው ያነሳው ህዝባዊ ጥያቄ በመሆኑ የአንድነት አመራሮችና አባላት መስዋዕት ቢሆኑም ህዝቡ ትግሉን ከዳር እንሚያደርሰው አንጠራጠርም፡፡
ነብዩን እናመሰግናለን፤ መንግስትን ጉርምስናውን በቅጡ አድርገው እንላለን!

No comments:

Post a Comment