Sunday 2 June 2013

ሰላማዊ ሰልፉን በርካቶች እየተቀላቀሉት ጉዞው ቀጥሏል፡፡ አቤ ቶክቻው!!

945572_464808363610792_1068741911_n ሰላማዊ ሰልፉን በርካቶች እየተቀላቀሉት ጉዞው ቀጥሏል፡፡
መንግስታችን ይህንን ሰልፍ ዕውቅና የሰጠው ሰማያዊዎቹ በአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ላይ እንደዛቱት ያደርጉትና አልተኩስ ነገር እንግዳ አለ አላስር ነገር ስንቱን አስሬ ብሎ ሰግቶ መሆኑ ይጠረጠራል፡፡
የሆነ ሆኖ ዛሬ በመንግስት ዕውቅና ያገኘ የተቃውሞ ሰልፍ እየተካሄደ ነው፡፡


 ከቀበና አራትኪሎ ከአራት ኪሎ ደግሞ ፒያሳ የተሰላፊው ቁጥር እየጨመረ ወደ ኩባ አደባባይ እየተጓዙ ይገኛሉ፡፡
935468_10201243961331252_914461716_nአንድ ወዳጄ እንዳወጋኝ መንግስት እስከዛሬ ድረስ በሚያደርጋቸው ሰልፎች ላይ ተማሪዎችን ከትምህርት ቤት አስወጥቶ ወደ ሰልፉ ያሰማራቸው ነበር፡፡ እንዳይቀሩም የስም ጥሪ እና ቁጥጥር ይደረጋል የቀረ ተማሪም ማርክ ይቀነስበታል፡፡

ዛሬ ሰማያዊ ፓርቲ ደግሞ ሰላማዊ ሰልፍ ሲጠራ ሁሉም ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቻቸውን በተለምዶ “ሜካፕ ክላስ” እንደሚባለው በሰንበቱ ለትምህርት ጠርተዋቸዋል፡፡ ተማሪዎቹ እንዳቀሩም ሃምሳ ማርክ እንደሚሰጣቸው ተነግሯቸዋል፡፡
አንድ ጊዜ መንግስት የሆነ ሰልፍ ጠርቶ እኔም ስታድም ተገንቼ ነበር፡፡ በሰልፉ ላይ አንዲት ሴትዮን እናቴ የዚህ ሰልፍ አላማ ምንድነው ስላቸው… እንጃ ልጄ አበሏ ትጠቅመኛለች ብዬ ነው ወጣሁት ስምጠሪው አንዴ ቢየኝ ወደቤቴ እመለስ ነበር ብለውኛል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ በጠራው ሰልፍ ላይ አበልም የለም ማርክም የለም፡፡ ሰዉ ግን አሁንም እየጎረፈ ነው፡፡
በዚህ ሰልፍ ላይ ጎልቶ ከወጣው ዜማ መካከል ሙስሊሙ ህብረተሰብ እና ሌላው በአንድ ድምፅ “አንለያይም አንለያይም… መቼም አንለያይም አንለያይም!” እያሉ ያዜሙበት ይገኛል፡፡
እደግመዋለሁ፤

“በሰላም ወጥታችሁ በደህና እንድትገቡ ይመኝላችኋል መላ ህብረተሰቡ”

No comments:

Post a Comment