Tuesday 22 January 2013

ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በደቡብ አፍሪካ ተቃውሞአቸውን አሰሙ

ጥር ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም  

ኢሳት ዜና:- በኢትዮጵያ እና በዛምቢያ መካከል የተካሄደውን የአፍሪካ ዋንጫ ተከትሎ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን የተለያዩ መፈክሮችን በመያዝ መንግስት በሙስሊም ኢትዮጵያውያን ላይ የሚወስደውን እርምጃ ተቃውመዋል።
 
 
ሙስሊሞቹ መሪዎቻችን ይፈቱ፣ በእምነታችን አንደራደርም፣ የሀይማኖት ነጻነት ይከበር፣ የሚሉ መፈክሮችን በእንግሊዝኛ በመጻፍ ለአለም የቴሌቪዥን ተመልካቾች አሳይተዋል።

ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ብሄራዊ ቡድኑን በከፍተኛ ስሜት ከመደገፍ አልፈው በእረፍት ሰአቶቻቸው ተቃውሞአቸውን ሲገልጹ ተስተውሎአል።

No comments:

Post a Comment